Sunday, December 20, 2015



ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ዓመታት ያከናወነቻቸው
የዘላቂ የቱሪዝም ልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀቁ፡፡
ከዓለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ብድር በኢትዮጵያ ዘላቂ የቱሪዝም ልማት ፕሮጀክት ላለፉት 6 ዓመታት በአክሱም፣ በላሊበላና በአዲስ አበባና አካባቢዋ ሲከናወኑ የነበሩ ስራዎች ተጠናቀዋል፡፡ 


የፕሮጀክቱን መጠናቀቅ ምክንያት በማድረግ በአክሱምና በላሊበላ የተሰሩ ስራዎች በመንግስት ከፍተኛ አመራሮች፣ የክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ቦርድ አባላትና እና ባለድርሻ አካላት ጎብኝተውታል፡፡
አካባቢዎቹን ለቱሪስት ምቹ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎች የተሰሩ ሲሆን ደረጃውን የተጠበቀ መፀዳጃ ቤት፣ መስቀል አደባባይ፣ ድልድዮች፣ መንገዶችን ለመኪና ምቹ የማድረግ ስራ ተሰርቷል፡፡
ፕሮጀክቱ ያከናወናቸው የተለያዩ የልማት ስራዎችም ከታህሳስ 9 እስከ ታህሳስ 11 ቀን 2008 ዓ.ም. ባሉት ጊዜያት ተጎብኝተዋል፡፡

No comments:

Post a Comment