Wednesday, April 18, 2012

Saturday, April 14, 2012


ዜና
ዛሬ ሚያዝያ 6 ቀን 2004 ዓ.ም

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሪት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ…. የመጨረሻ ቀን

ቀዳማዊት እመቤት አዜብ መስፍን ከየኔታ መኖሪያ ቤት/አልፋ ቪላ/ እስከ ዞር ኃይሎች በእግር በመጓዝ ሸኝተዋል፤

ስራቸው ህያው በመሆኑ ቀብር ሳይሆን ሽኝት ነበር፤

በሽኝቱ በርካታ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣አምባሳደሮች፣የሙያ ልጆቻቸውና አድናቂዎቻቸው ተገኝተዋል፡፡


እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሪት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ…. በሚወዳቸው፣በሚያከብራቸውና ዘመናቸውን ስለ ክብሩ በኖሩለት የኢትዮጵያ ህዝብ ለዘለዓለም ተሸኝተዋል፡፡ ለስምንት አስርት ዓመታት የኖሩባት ኢትዮጵያ የኖሩላትን ያክል ውለታቸውን ባትመልስም፣ አፍቅረዋታል….ፍቅራቸው ደግሞ የአፍ አልነበረም፣ ገልጸውታል…..ትውልድ የሚጋራውን ፍቅር…. ህይወት ዘርተውበታል፡፡