Thursday, November 15, 2012


ዓለም አቀፍ የመቻቻል ቀን ዛሬ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር በሃገር አቀፍ ደረጃ ተከበረ!!!

በመድረኩ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበዋል፡፡

ዓለም በብዝሃነቷ የሚያውቃትን ያክል አብሮ የመኖርና የመተሳሰር እሴቶቿ ጎልተው ከወጡ ሃገራት መካከልም ትልቅ ስፍራ ይሰጣታል፡፡ ከመቻቻል ይልቅ  ከፍጹም ፍቅር በመነሳት አንዱ ለሌላው የሚኖርባት የወንድማማቾች ምድር የሆነችው ኢትዮጵያ እነሆ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ሃገር አቀፍ የመቻቻል ቀንን አክብራለች፡፡

ዛሬ በብሔራዊ ቲያትር በተዘጋጀው ሲምፖዚየም ላይ የተገኙት የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ዳውድ መሐመድ አለመቻቻል አስከፊነቱና የሚፈጥረውን ስጋት ለመቀነስ የሁሉንም ዜጎች ቁርጠኝነት በየጊዜው ለማደስ ይህን ዝግጅት ማዘጋጀቱ አስፈላጊ እንደሆነ በእለቱ ዝግጅቱን ሲከፍቱ ባደረጉት ንግግር ገልጸዋል፡፡

አቶ አውላቸው ሹምነካ በሚኒስቴር መስሪያቤቱ የቋንቋና የባህል እሴቶች ልማት ዳይሮክተሬት ዳይሬክተር ዘንድሮ የሚከበረው በዓል የመቻቻል ባህላችንን በማጉላት ለዓለም ተምሳሌት  እንሆናለን በሚል መሪ ቃል  እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በእለቱ ዶ/ር ሀሰን ሰይድ፣ አቶ ተመስጌን ዩሐንስ፣  አቶ መርከብ መኩሪያ፣ አቶ ተሾመ ብረሃኑ ከማል ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረቡ ሲሆን ረዳት ፕሮፌሰር አህመድ ዘካሪያ ውይይቱን መርተውታል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የታደመው እንግዳ ከወትሮው በተለየ በርካታ እና ዝግጅቱም በብሄራዊ ቲያትር ባህል ቡድን የተዋዛ ነበር፡፡