Saturday, September 22, 2012


የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባህልና ቱሪዝም መምሪያዎችና ጽ/ቤቶች በባህር ዳር ከተማ ከትመው የዓመቱን አፈጻጸም ገመገሙ!

ጎንደር 1ኛ ደረጃነቷን  አስጠብቃለች፡፡

ምስራቅ ጎጃምና አዊ ዞን ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ይዘዋል፡፡


ከመስከረም 7 ቀን ጀምሮ እስከ ዛሬ መስከረም 12 ቀን 2005 ዓ.ም ባህርዳር የተሰበሰቡት የባህልና ቱሪዝም ሴክተር ተቋማት በዋናነት ዓመታዊውን አፈጻጸማቸውን የገመገሙ ሲሆን መርሀ-ግብሩ በክልሉ ባህል፣ቱሪዝምና ፓርኮች ልማት ቢሮ የተዘጋጀ ነው፡፡

በአፈጻጸም ደረጃ ከአዲስ አበባና ከድሬዳዋ ቀጥሎ የቱሪዝም ዳይሮክተሪዋን ባስመረቀች ማግስት የጎንደር ከተማ አስተዳደር አንደኛ ደረጃን ይዛለች፡፡ በተያዘው ዓመት አያሌ የተለዮ ተግባራትን ያከናወነችው ጎንደር ከአዲስ አበባ ቀጥሎ የሙዚየም ቀን ተከብሮባታል፡፡ ከአማርኛ ቋንቋ ባሻገር በትግራይ በነበረው የከተሞች ቀን ላይ በትግርኛ ቋንቋ በተዘጋጁ የፕሮሞሽናል ቁሳቁሶች እራሷን ያስተዋወቀችው ጎንደር፤ በዚሁ ዓመት የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ባለድርሻዎችን ያካተተ የቱሪዝም ገቢ አመንጪ ኮሚቴ በማቋቋም ወደ ስራ የገባችበት ዓመት ነበር፡፡


Friday, September 14, 2012

tuba

መስቀል በአዲግራት

መስቀል በአዲግራት
 
መስቀል በሃገራችን በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት አንዱ ነው፡፡ በተለይም የደመራ በዓል ከፌስቲቫል ቱሪዝም ሀብታችን ውስጥ ግንባር ቀደሙን ቦታ ይይዛል፡፡ ይህንን በዓል የሰው ልጆች ሁሉ እሴት ለማድረግም ጥረቶች ተጀምረዋል፡፡ መስቀልን በዩኔስኮ ለመመዝገብ በቅቷል፡፡

መስቀል እንደ የኢትዮጵያውያን እሴትና ባህል ከዳር ዳር የሚከበር ከአደይ ጋር አብሮ የሚፈካ፣ ከዘመን ጋር የሚጠባ በዓል በመሆኑ ይበልጥ ደማቅ እንዲሆን አድርገዋለል፡፡

በድንቅ እሴት የተሞላውና ብዙ ሳይነገርለት የኖረው የምስራቃዊ ትግራይ ዞን የመስቀል በዓል አንዴ ሌላ የባህል ሃብት መስህባችን ነው፡፡