Tuesday, August 26, 2014


         አሸንዳ - የሰሜናዊቷ ኮከብ ከተማ ኮከብ ኩነት

 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች ዘንድ የጾመ ፍልሰታ ፍጻሜን ተከትሎ የሚከበረው የአሸንድዬ በዓል በዋናነት በሰሜን ኢትዮጵያ ከሚከበሩ መንፈሳዊ በዓላት መካከል የሚጠቀስ ነው፡፡ የአሸንዳ ባህላዊ ጨዋታ መጠሪያ የኾነው ቄጤማ ረዥምና ለምለም እንደ ቅጠል ሰፋ ያለ ሲሆን ቁመቱ 80 እስከ 90 . ይኾናል፡፡

የአሸንዳ በዓል በትግራይ ብሔራዊ ክልል የሚከበር በሀገራችን ከሚገኙ ኩነቶች አንዱ ነው፡፡ አሸንዳ ጥንታዊና የልጃገረዶች ባህላዊ በዓል ነው፡፡ በተለይም ከአዲስ አበባ በ783 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው የክልሉ መዲና መቐለ በየዓመቱ የምታስተናግደው ይህ ፌስቲቫል ከትግራይ ወጣቶች ባለፈ ጎብኚዎችም በጉጉት የሚጠብቁት ባህላዊ ትዕይንት ሆኗል፡፡

Thursday, August 21, 2014


የአሸንዳ በዓል ዓመታዊ ኩነት በሰሜናዊቷ መቐለ መከበር ጀምሯል፡፡

ቱባ-መቐለ
 

በየዓመቱ የአሸንዳ በዓል በድምቀት የሚከበርባት የትግራይ ክልል መዲና ዘንድሮም በተመሳሳይ መልኩ በዓሉን ለማክበር ሰፊ ዝግጅት ስታደርግ ቆይታለች፡፡ ዛሬ ነሐሴ 15 ቀን 2006 ዓ.ም የአሸንዳ በዓል ዓመታዊ ኩነት ጀምሯል፡፡ ጠዋት በሚላኖ ሆቴል ለግማሽ ቀን በአሸንዳ ላይ የመከረው ሲምፖዚየምም የዚሁ ዝግጅት አካልና በትግራይ ባህልና ቱሪዝም ኤጀንሲ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከሰዓት ደግሞ የመቐለ ጎዳናዎች በአሸንዳ ጨፋሪዎች ይደምቃሉ፡፡ ነገ የሚከናወነው ዋናው የአሸንዳ በዓል ዝግጅት ነው፡፡
 

Friday, August 8, 2014


የፎቶና ቪዲዮ ባለሙያዊ አዚዝ አህመድ ድንቅ ሥራዎች ተመረቁ፡፡
 

ፕሮፌሽናል የጉዞ ፎቶ ግራፈሩና የቪዲዮ ባለሙያ የሆነው አዚዝ አህመድ በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ያነሳቸው የአእዋፍ ፎቶ ምስሎችና የሀገራችንን የተፈጥሮ ሀብቶች የሚያሳየውን የአጭር ድምጽና ምስል የቱሪዝም ዘጋቢ ፊልሙን ትናንት ነሐሴ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 9፡30 ላይ በአዲስ አበባ ካፒታል ሆቴል አስመርቋል፡፡

ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ይህ በኢትዮጵያዊ በዚህ መልኩ ሲሰራ የመጀመሪያ ሊባል የሚችለው ድንቅ ስራ ክቡር አቶ አሚን አብዱልቃድር የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ ክቡር አቶ እውነቱ ብላታ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ እንዲሁም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ዶ/ር ይናገር ደሴ በተገኙበት ተመርቋል፡፡

የጉዞ ፎቶግራፈሩ ጥንካሬ እውን ያደረጋቸው እነኚህ የኢትዮጵያን እምቅ የተፈጥሮ መስህቦች የሚያስተዋውቁ ስራዎች በሀገራችን ቱሪዝም ልማት ጎብኚዎችን በመሳብ የሚኖራቸው ፋይዳ ከፍተኛ ነው፡፡ ዶክመንተሪውም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአየር መንገደኞች በመቅረብ ላይ ያለ መሆኑን ስራውን ከደገፉት አንዱ የሆኑት የፍራንክፈርት ዙኦሎጂካል ሶሳይቲ ሃላፊ ዶ/ር ዘላለም ገልጸዋል፡፡

አዚዝ አህመድ በተለየ መልኩ ትኩረታቸውን በአእዋፍና ተፈጥሮ መስህቦች ዙሪያ አድርጎ በመስራት ስኬታማ ከሆኑ ኢትዮጵያዊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች አንዱ ነው፡፡