Saturday, February 3, 2018

የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማህበር 78ተኛ ዓመታዊ የፈረስ ትርዒት ነገ ይካሄዳል፡፡


በአዊ ብሔረሰብ ዞን በየዓመቱ የሚከበረውና በሰባት ቤት አገው ፈረሰኞች ማህበር የሚዘጋጀው ዓመታዊ የፈረስ ትርዒት ዘንድሮ ለ 78ተኛ ጊዜ ነገ ጥር 27 2010 ዓ.ም. በእንጅባራ ከተማ በድምቀት ይካሔዳል፡፡


በ 1933 ዓ.ም. በአደዋ ጦርነት የዘመተውን የፈረሰኛው ጊዮርጊስ ታቦትና የፈረሰኛ አርበኞችን ተጋድሎ ለመዘከር በኢጣሊያ ወረራ ወቅት የተፀነሰው የአዊ ፈረሰኞች ማህበር ለ 78 ተከታታይ ዓመታት ባህላዊ የፈረስ ትርዒት ሲያዘጋጅ ቆይቷል ዘንድሮም የአማራ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከፌደራል ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴርና ባለድርሻ አካላት በመተባበር የደገፉት ይህ በዓል በአዊ ብሔረሰብ ዞን ዋና ከተማ እንጅባራ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል፡፡