Friday, August 26, 2016


አሸንዳ 2008 በዓል በመቐለ በድምቀት ተከብሯል፡፡
Photo; Ashenda festival in Mekelle

አሸንዳ 2008 ባህላዊ ኩነት በትግራይ ክልል ርዕሰ መዲና በመቐለ በድምቀት ተከብሯል፡፡ ከነሐሴ 15 እስከ ነሐሴ 18 ቀን 2008 ዓ.ም. በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ሲከበር የቆየው ይህ በዓል ከመቐለ ከተማ ውጪ በተንቤን አብይ አዲም በድምቀት መከበሩን ለማወቅ ችለናል፡፡


ሻደይ 2008 ፌስቲቫል በድምቀት ተከበረ፡፡
Photo: shaday festival 2016 wagehimera zone
ሻደይ 2008 የባህል ፌስቲቫል በዋግኽምራ ብሔረሰብ ዞን መዲና በሰቆጣ ከተማ ከነሐሴ 14 ቀን እስከ 16 2008 ዓ.ም. በድምቀት ተከብሯል፡፡"የሻደይ ባህላችን ለዘላቂ ልማታችን" በሚል የተከበረው ይህ በዓል የተለያዩ ዝግጅቶችን ያካተተ ሲሆን በርካታ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላችው እንግዶች የታደሙበት ነው፡፡

Thursday, August 4, 2016


                       ኦይዳ ወረዳ
 

የኦይዳ ወረዳ በጋሞ ጎፋ ዞን ከሚገኙ አስራ አምስት ወረዳዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን የወረዳው ዋና ከተማ ሸፊቴ ይባላል፡፡ ወረዳው የተመሰረተው በ1998 ዓ.ም. ነው፡፡ ኦይዳ ማለት ለም ማለት ሲሆን የብሔረሰቡና የወረዳው መጠሪያም ነው፡፡ ወረዳው በሃያ ቀበሌያት የተዋቀረ ሆኖ በደቡብ ኡባ ደብረ ፀሀይ፣ በሰሜን ገዜ ጎፋ፣ በምዕራብ ሰሜን አሪ እና በምስራቅ ደግሞ ደንባ ጎፋ ወረዳ ያዋስኑታል፡፡

Wednesday, August 3, 2016


        የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የህዝብና ዓለም አቀፍ ዳይሮክተሬት በ2008 ዓ.ም. አፈጻጸም ተሸላሚ ሆነ፡፡

በመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት በዘርፍ ከሚገኙ የፌዴራል የኮሙኒኬሽን አደረጃጀቶች መካከል የ2008 ዓ.ም. አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላመጡ እውቅና ተሰጥቷል፡፡