Friday, January 25, 2013


የዛይ ማህበረሰብ የትንሣኤ ዘመን

ዝዋይ የሚለው ቃል ትርጉም ዛይ ከሚለው የደሴቶቹ ማህበረሰብ መጣ የሚሉ አፈ-ታሪኮች በርካታ ናቸው፡፡ የዝዋይ ደሴቶች እጅግ በርካታ ምሁራንን አፍርተዋል፤ ከዚህ ዓልፎ እንደ ግርሀም ሀንኮክና ጀምስ ብሩስ ባሉ የጉዞ ጸሐፍት የተተረከላቸው እነኚህ ደሴቶች ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር የጠበቀ ሚስጥራዊ ግንኙነት ያላቸው ናቸው፡፡ ታቦተ ጽዩን በስደቷ ወቅት ያረፈችበት ስፍራ በመሆኑ ብዙዎች ለበረከት ይተማሉ፡፡