Tuesday, February 23, 2016


በአፍ መፍቻ ቋንቋ የመናገር ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ በሰቆጣ ከተማ ተከበረ፡፡
 

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባል ሀገራት ከሚያከብሯቸው በዓላት አንዱ የሆነው በአፍ መፍቻ ቋንቋ የመናገር ቀን ነው፡፡ ይህ ቀን በኢትዮጵያም በየዓመቱ በተለያዩ አካባቢዎች ሲከበር ቆይቷል፡፡ የዘንድሮው በዓል በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሔረሰብ ዞን ከአዲስ አበባ በ720 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሰቆጣ ከተማ ከየካቲት 13-15/2008 ዓ.ም. ተከብሯል፡፡

ለ74ኛ ጊዜ የተካሄደው የኦሮሞ ብሔር የጉጂ የገዳ ሥርዓት የስልጣን ሽግግር በደመቀ ሥነ-ሥርዓት ተከናወነ፡፡
 

በኦሮሞ ብሔር ባህል በየስምንት ዓመቱ የሚከናወነው የገዳ ሥርዓት የስልጣን ሽግግር ለ74ኛ ጊዜ እጅግ በደመቀ ሥነ-ሥርዓት በጉጂ ዞን ሜኤ ቦኮ የካቲት 13 ቀን 2008 ዓ.ም. ተካሂዷል፡፡

Wednesday, February 17, 2016

አባ ገዳ ቱር የብስክሌት ተወዳዳሪዎች ዛሬ እኩለ ቀን መኤ ቦኮ ደረሱ፡፡
አባ ገዳ ቱር የብስክሌት ተወዳዳሪዎች ዛሬ እኩለ ቀን መኤ ቦኮ ሲደርሱ የገዳ አካላት ከጉሚ እየወጡ ነበር፡፡ አዲስ አበባ ከሚገኘዉ ከኦሮሞ ባህል ማዕከል በትናንትናው ዕለት ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት የተንቀሳቀሱት ስምንት ሴቶችና አስራ አምስት ወንድ ተወዳዳሪዎች በአጠቃላይ 32 ልኡካንን ይዘዉ እንደመጡ የገለጹት የዝግጅቱ አስተባባሪ አቶ ግዛዉ ተወዳዳሪዎቹ ከኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ዞንና ወረዳዎች ተመልምለው የመጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በጉጂ ኦሮሞ በበደለናና በሀርሙፋ አባገዳዎች መካከል የካቲት 13ቀን ለሚደረገዉ የስልጣን ሽግግር ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡