Thursday, October 20, 2016



አዲሱ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ብራንድ እና ቀጣዩ የመገናኛ ብዙኃን ሚና

=====================================
ኢትዮጵያ የመለዮ ስያሜውን LAND OF ORIGINS ያደረገ አዲስ የቱሪዝም አርማ እና መለዮ ስያሜ ይፋ አድርጋለች፡፡ በቅርቡ በኢትዮጵያ ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጉት አዲሱ የመለዮ ስያሜ ግማሽ ምዕተ ዓመት ያክል የአስራ ሦስት ወር ጸጋ በሚል ሲያገለግል የኖረውን ብራንድ ስያሜ የሚተካ ነው፡፡

Friday, October 14, 2016


የመስቀል በዓል አከባበር በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ
ጢያ ትክል ድንጋይ-ሶዶ ወረዳ
 

የመስቀል በዓል የተራራቁ የሚቀራረቡበት፣ የተነፋፈቁ ናፍቆታቸውን የሚወጡበት፣ ያለፈው ጊዜ ምን እንደሚመስል መጪው ጊዜ ምን መሆን እንዳለበት የሚወስኑበት ለክብረ በዓሉ በሰላም ላደረሳቸው ፈጣሪያቸው ምስጋና የሚያቀርቡበት ለወደፊቱም መልካም ምኞታቸውን የሚገልፁበት አጋጣሚ ነው፡፡ መስቀል የክስታኔ ቤተ-ጉራጌ ማህበረሰባዊ ልማዱን ከትውልድ ትውልድ ከሚያስተላልፍባቸው ሀገራዊ ልማዶች መካከል አንዱ በዓል ነው፡፡