Monday, May 27, 2013


ኮንሶ…….

የኮንሶ ህዝብ ገናና ነው፡፡ ስራ ስሙን ከፍ አድርጎት ከጥንት እስከ ዛሬ ብዙ ይወራለታል፡፡ የወረዳ ስያሜ በብሔረሰቡ መጠሪያ ስም ኮንሶ ይባላል፡፡ በደቡብ ክልል ሲገኝ በባህል ቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ መዳረሻ እየሆነ በመጣው የደቡብ ኦሞ በራፍ የሚገኝ አካባቢ ነው፡፡
ኮንሶ- ካራት
 
አዲሲቷ ሰገን አካባቢ ህዝቦች ዞን ሥር ከሚገኙ አምስት ወረዳዎች አንዱ የሆነው ኮንሶ ወረዳ  ከአዲስ አበባ በ595 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ከሀዋሳ ደግሞ በ365 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ በደቡባዊ ምስራቅ ቀጠና ይገኛል፡፡ ለደቡብ ኦሞ ጅንካ ከተማና  ለያቤሎ ሞያሌ መስመር ቀጠና መሆኑ የንግድ ማእከል እንዲሆንም አድርጎታል፡፡

የሲዳማ ዞን የቱሪስት መዳረሻዎች
BONORA FALL-SIDAMA
 

ሎካ አባያ ብሔራዊ ፓርክ

ሎካ አባያ ብሔራዊ ፓርክ በሲዳማ ዞን የሚገኝ ለዞኑ ብቸኛ ብሔራዊ ፓርክ ነው፡፡ ፓርኩ በሎካ አባያ ወረዳ ከሐዋሳ ከተማ 73 ኪሎ ሜትር  እና ከሎካ አባያ ወረዳ ዋና ከተማ ከሀንጣጤ 13 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል ፡፡ ፓርኩ በታላቁ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ /Great east African rifty vally/ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን የሞቃት አየር ንብረት ማለትም ወደ በረሃማ የተጠጋ የስነ - ምህዳር ባህሪ ይታይበታል፡፡ የታላቁ ምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ስነ-ምህዳር Great east African rifty vally system አካል የሆነው የአባያ ሐይቅ የዚህ ፓርክ አካል ነው፡፡ የአባያ ሀይቅን ጨምሮ ብላቴ ወንዝ ፣ጊዳዎ ወንዝ እና ኮላ ወንዝ በዚህ ስፍራ መኖራቸው ለፓርኩ የተለያዩ ብዝሃ ህይወት /bio-diversity/ እንዲኖሩት አድርጎታል ፡፡


አፍሪካና ቱሪዝም

የዛሬ 50 ዓመት ከመነጣጠል አንድነትን የመረጡት አፍሪካውያን ግማሽ ምእተ አመት የሚሆን የጋራ ጉዞ አድርገዋል፡፡ ዘንድሮ ይህንን ልደት መዲናችን አዲስ አበባ እያከበረችው ነው፡፡ ይህንን ታላቅ ዝግጅት ምክንያት አድርገን አፍሪካና ቱሪዝምን ለመቃኘት ወደድን፡፡
African un
 

አህጉራችን አፍሪካ በቀላሉ የሚጋዙ ሀብቶቿን በቀኝ ግዛት ዘመን ቢበዘበዝባትም፡፡ ተፈጥሮ የለገሰቻት ተወስዶ የማያልቀው ጸጋዋ ግን ዛሬም የትናንት ቀኝ ገዢ ሀገራትን በስጎመዠ መልኩ እንደነበር አለ፡፡ አፍሪካ አሁን የዓለም ጎብኚዎች መዳረሻ እየሆነች ነው፡፡ ሀምሳ አራት ገደማ ሀገራት የተጠለሉባት ይህች አህጉር እንደ ኪሊማንጃሮ ካሉ ተራሮች እስከ ዝቅተኛው የምድር አካል ዳሉል ድረስ የተካተተባት ምድር ናት፡፡ ታላቁ የሰሀራ በርሐ መገኛ አፍሪካ ነው፡፡ በሰው ልጅ ታሪክ የተለየ ቦታ ካላቸው የተፈጥሮ ሀብቶች አንዱ የሆነውና ረጅሙ ወንዝ ናይል የአፍሪካውያን ነው፡፡

Monday, May 20, 2013


ኮንሶ ፌስቲቫል 2005



                                ኮንሶ ፌስቲቫል 2005