Sunday, August 12, 2018


የኢትዮጵያ ብሔራዊ የባህል ማዕከል በሀገረ ሰብ የባህል ሕክምና ዙሪያ ሀገራዊ የውይይት መድረክ አዘጋጀ፡፡
የባህል መድኃኒት ጠበብቶች እና ሳይንሳዊ ሊቃውንቶች ተቀራርቦ መስራት ላይ ችግር እንዳለባቸው ተገልጾዋል፡፡
*******


የኢትዮጵያ ብሔራዊ የባህል ማዕከል ነሐሴ 4 ቀን 2010 ዓ.ም. አምስት ኪሎ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን አዳራሽ በሀገረሰባዊ ሕክምና ዙሪያ ሀገራዊ ውይይት አካሄደ፡፡ ውይይቱ ሀገረሰባዊ የህክምና ጥበባችን ከየት? ወደየት? በሚል መነሻ የቀረበ ሲሆን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መድሃኒት መምህራን ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጥናት አቅርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡፡