Tuesday, August 21, 2012


ኢትዮጵያ በብሄራዊ ሀዘን ላይ ትገኛለች፤

የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አስክሬን ትናንት ምሽት ነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም አዲስ አበባ ገብቷል፤

መንግስት መደበኛ የመንግስት ስራ ሳይዘጋ የሃዘን አዋጁ እንዲቀጥል አውጇል፤

ላለፍት 21 ዓመታት ሃገሪቱን በግንባር ቀደምነት ሲመሩ የነበሩት፤ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአህጉሪቱ ወሳኝ ጉዳዮች ዓለም አቀፋዊ መድረኮችን የሚታደሙት፤የኢ.ፊ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር፤ የኢህአዴግ ሊቀ-መንበር፤ አቶ መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የሃገራችን መንግስት ነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም ለህዝቡ አስታውቋል፡፡

ሰኞ ለማክሰኞ ዋዜማ ከእኩለ ለሊቱ በፊት መሞታቸው የተነገረው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በስልጣን ላይ በቆዩባቸው 21 ዓመታት የሚመሩት መንግስት ሀገራችን የቱሪዝምና የባህል ፖሊሲዎች እንዲኖሯት በማድረግ፣በውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ስኬት የኮንፈረንስ ቱሪዝም እንዲስፋፋ፣ አዳዲስ ፓርኮች እንዲለሙ፣ ቅርሶች የቅርሱ ባለቤት የሆነው ህዝብ እንዲያስተዳድራቸው በማድረግ እና የቱሪዝም ልማቱን የሚያግዝ የብድር ስምምነት በማድረግ ዘላቂ የቱሪዝም ልማት ላይ በማተኮር፣ በርካታ የባህል ልውውጥ መድረኮችን ሀገራችን እንድትሳተፍ በማስቻል ያበረከቷቸው ተግባራት የሚወደሱ ናቸው፡፡

የሀገሬ ሚዲያ ኮሙኒኬሽን እና የቱባ መጽሔት ባልደረቦች በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማንን ሀዘን እየገለጽን ለባለቤታቸው፣ለትግል ጓዶቻቸው እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን፡፡

Monday, August 20, 2012


ብጹእ ወቅዱስ ዶ/ር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማይ፤ ፓትረያሪክ ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ሊቀ-ጳጳስ ዘ አክሱም፤ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ፕሬዝዳንት፤ የዓለም ሐይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዝዳንት፤ የሰላም አምባሳደር በተወለዱ በ76 ዓመታቸው አረፍ፤



ለሃገሪቱ ቱሪዝም ልማት እና ለሙዚየሞች መስፋፋት ትልቅ አስተዋጾ ማበርከት የቻሉ አባት ነበሩ፤



የዛሬ 76 ዓመት በአድዋ ከተማ አቅራቢያ በአባ ገሪማ ገዳም አካባቢ ጥቅምት 25 ቀን 1928 ..  ከካህን ቤተሰብ፣ ከአባታቸው ከአፈ መምህር ገብረ ዮሐንስ ወልደ ሥላሴና ከእናታቸው ከወ/ አራደች ተድላ ተወለዱ፤ የያኔው ገብረ መድኅን የአሁኑ  አቡነ ጳውሎስ፣ከዚያም  በጥንታዊው አባ ገሪማ ገዳምና በአዲስ አበባ ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መንፈሳዊ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ ወደ አሜሪካ በማቅናትም ከሩሲያው የቅዱስ ቭላድሚር ቲኦሎጂካል ሴሚናሪ በኦርየንታልና በምሥራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት መካከል ባለው የነገረ መለኮት ይትበሐል (ትምህርት) 1954 . ዲፕሎማ አግኝተዋል፡፡ ቀጥሎም በየል ዩኒቨርሲቲ በኦሪየንታል፣ በምሥራቅና በምዕራባውያን አብያተ ክርስቲያናት መካከል ስላለው የነገረ መለኮት ትምህርት አመለካከትና ልዩነት ባችለር ኦፍ ዲቪኒቲ ዲግሪን 1958 . ሲያገኙ፣ ከፕሪንስተን ዩኒቨርሲቲ በክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ማስተርስ ኦፍ ቴኦሎጂ ዲግሪን 1964 .. ተቀብለዋል፡፡ በዚያው ዩኒቨርሲቲ 1980 .. የዶክትሬት (ፒኤችዲ) ዲግሪያቸውን ያገኙት ስለእግዚአብሔር ህልውና እና ስለፍልሰታ ማርያም በጻፏቸው የጥናት ድርሳኖች ነው፡፡

Thursday, August 9, 2012


የሲዳማ ዘመን መለወጫ /ፍቼ/ በአል አከባበር

ከይረጋዓለም ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር


ፍቼ በዓል በሲዳማ
ፎቶ ከሲዳማ ባ/ቱ/መ/ኮ/መምሪያ

“ፍቼ” በሲዳማ ባህል ከትውልድ ትውልድ ሲተላለፍ የቆየ የዘመን መለወጫ በአል ነው፡፡ በአሉ ከሁለት ሳምንት ላላነሰ ጊዜ በድምቀት የሚከበር ሲሆን አከባበሩም ቅደም ተከተላዊ ሂደትና በደረጃ እየሰፋ የሚሄድ የጋራ የአከባበር አድምታ ያለው ነው፡፡ ስለሆነም ፍቼ በቤተሰብ ወይም በጎረቤት ደረጃ ተሰባስቦ በማክበር የሚያበቃ ሳይሆን ከዚህም በሰፋ መልኩ በባህላዊ አደባባይ /ጉዱማሌ/ በጋራ በድምቀት የማክበር ሂደትን ያካትታል፡፡ ለአከባበሩ እያንዳንዱ ቤተሰብ በቅድሚያ እንደ አቅሙ ቅድመ ዝግጅት ያደርጋል፡፡ ከዚሁ አንጻር የቤቱ እመቤት ለበአሉ ቅቤ ታጠራቅማለች ወተት በታጠነ ማለፊያ “ቁሹና” /የወተት እቃ/ ታከማቻለች የእንሰት ውጤት የሆነውን ቆጮ ለበአሉ በሚሆን መጠንና ጥራት ከወዲሁ ታሰናዳለች፡፡