Wednesday, September 17, 2014


የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኒዓለም ሙዚየም
የልጅ እያሱ አልጋ
 

አዲስ አበባ ከሚገኙ 14 ሙዚየሞች አንዱ የቀጨኔ ሙዚየም ነው፡፡ ቀጨኔ ሙዚየም በአስተዳደር ጊዜያቸው ለህብረተሰቡ ኑሮ ምቹ ከመሆናቸው የተነሳ አቤቶ (ማር) የሚል ስያሜ የተሰጣቸው ልጅ እያሱ ከመቶ ዓመት በፊት  ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ካሳነፁ በኋላ የተቋቋመ ሙዚየም ነው፡፡ በሙዚየሙ ውስጥ ከሚገኙ ቅርሶች ብዙዎቹ የልጅ እያሱ የግል መገልገያ እቃዎች፣ ነዋየ ቅድሳት፣ አልባሳት እና የተለያዩ ነገስታት ስጦታዎች ይገኛሉ፡፡

በናና ጸማይ…..


 
በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ደቡብ ኦሞ ዞን ስር ከተዋቀሩት 8 ወረዳዎችና አንድ የከተማ አስተዳደር መካከል የበናና ፀማይ ወረዳ አንዱነው፡፡ የወረዳው ዋና ከተማ ቀይ አፈር ከዞኑ ዋና ከተማ ጂንካ በስተደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ በ42 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ወረዳው በሰሜን ከደቡብ አሪ እና ማሌ፣ በደቡብ ከሐመር ወረዳ፣ በስተምስራቅ ከኮንሶ በምዕራብ ከማጎ ፓርክ እና ሳላማጎ ወረዳ ጋር ይዋሰናል፡፡ በዞኑ ከሚገኙት 16 ብሔረሰቦች ውስጥ በዋናነት ሶስቱ ብሔረሰቦች የሚገኙት በዚህ ወረዳ ውስጥ ነው፡፡ እነዚህም የበና፣ የፀማይ እና የብራይሌ ብሔረሰቦች ናቸው፡፡

አፋር ያልተነገረላቸው ሁሉ አቀፍ የቱሪስት መስህቦች ቀጠና

የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በኢትዮጵያ ከሚገኙ 9 ክልሎችና 2 ከተማ መስተዳደሮች አንዱ ነው፡፡ ክልሉ ጂኦግራፊካሊ በሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያ በ39 14 እና 42 28 ሰሜን የኬክሮስ መስመርና በ8 49 እና በ14 30 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመሮች ይገኛል፡፡
Afar-
 

የአፋር ክልል በ5 አስተዳደራዊ ዞኖች 31 ወረዳዎችና በ1 ልዩ ወረዳ የተዋቀረ ነው፡፡ የቆዳ ስፋቱም 96,256 ስኩየር ኪ.ሜ ነው፡፡  እንደ ኢትዮጵያ ማእከላዊ ስታስቲክስ 2007 መረጃ መሰረት 1,411,920 ህዝብ ይኖርበታል፡፡ ከዚህም 86.6% በገጠር ቀሪው በከተማ የሚኖር ህዝብ ነው፡፡ አፋርኛ ቋንቋ የክልሉ የስራ ቋንቋ ሲሆን 90.8% ተናጋሪዎች አሉት፡፡