Monday, August 31, 2015

መስቀልን በደምባ ጎፋ
ጎፋ ጋዜ ማስቃላ፤
ከመስከረም 9-10/2008 ዓ.ም.

በሳውላ ከተማ

አገር አቀፍ የፋሽን ትርዒት፣ ባዛርና አውደ ርዕይ ሊካሄድ ነው፡፡




የባህል ቱሪዝም ሚኒስቴር የባህል ኢንዱስትሪ ልማት ትብብር ዳይሬክቶሬት፣የፋሽንና ዲዛይነሮች ማህበራትና ሜኖናይት ኢኮኖሚክ ዴቨሎፕመንት አሶሴሽን / MEDA/ በመተባበር የኢትዮጵያ ፋሽን አዲስ  ገልፅታ /New Images of Ethiopian Sustainable Fashion/ በሚል መሪ ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ከተለያዩ ክልሎች የባህል ልብስ አምራቾች ፤ ዲዛይነሮች ሌሎች መሰል አካላት ባሳተፈ መልኩ አገር አቀፍ የፋሽን ትርት፤ ባዛርና አውደ ርዕይ ከነሐሴ 26 እስከ ነሐሴ 30 2007 ዓ.ም በኦሮሞ የባህል ማዕከል ይከናወናል፡፡


Wednesday, August 19, 2015

ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ስትጨርስ፤
ዓመታዊ የጎብኚዎቿን ቁጥር 2.16 ሚሊዮን ለማድረስ አቅዳለች፡፡
በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣው የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ገቢ እያስገኘ መጥቷል፡፡ የፈረንጆቹ 2012 ዓመት 1 ቢሊዮን ያክል ጎብኚ የቱሪስት ፍሰት ተመዝግቦ 1.03 ትሪሊየን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡ ከዚህ ውስጥ በዚሁ ዓመት አፍሪካ ድርሻ 34 ቢሊዮን ዶላር ነበር፡፡ ሀገራችን የመጀመሪያውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ስታጠናቅቅ በ750 ሺ የውጪ ጎብኚዎች ተጎብኝታ ያገኘችው ገቢ 2 ቢሊየን ብር ደርሶ ነበር፡፡

Tuesday, August 18, 2015

የሆቴሎች የኮኮብ ደረጃ ምደባ ውጤት ይፋ ሆነ፡፡
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከተባበሩት መንግስታት የዓለም የቱሪዝም ድርጅት ጋር በመሆን ከሚያዚያ 1ቀን 2007ዓ.ም ጀምሮ በአገራችን የሚገኙ ሆቴሎችና ሪዞርት ላይ በኮኮብ ደረጃ የመመደብ ስራ የጀመረ ሲሆን በቅድሚያም በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ሆቴሎች ላይ የደረጃ ምደባ ስራው ተከናውኗል፡፡ በዚህም መሰረት በኮኮብ ደረጃ የመመደቡ ስራ ተጠናቆ ውጤቱ ነሐሴ 2,2007 ዓ.ም ለህዝብ ይፋ ሆኗል፡፡