Tuesday, August 21, 2012


ኢትዮጵያ በብሄራዊ ሀዘን ላይ ትገኛለች፤

የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አስክሬን ትናንት ምሽት ነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም አዲስ አበባ ገብቷል፤

መንግስት መደበኛ የመንግስት ስራ ሳይዘጋ የሃዘን አዋጁ እንዲቀጥል አውጇል፤

ላለፍት 21 ዓመታት ሃገሪቱን በግንባር ቀደምነት ሲመሩ የነበሩት፤ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአህጉሪቱ ወሳኝ ጉዳዮች ዓለም አቀፋዊ መድረኮችን የሚታደሙት፤የኢ.ፊ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር፤ የኢህአዴግ ሊቀ-መንበር፤ አቶ መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የሃገራችን መንግስት ነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም ለህዝቡ አስታውቋል፡፡

ሰኞ ለማክሰኞ ዋዜማ ከእኩለ ለሊቱ በፊት መሞታቸው የተነገረው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በስልጣን ላይ በቆዩባቸው 21 ዓመታት የሚመሩት መንግስት ሀገራችን የቱሪዝምና የባህል ፖሊሲዎች እንዲኖሯት በማድረግ፣በውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ስኬት የኮንፈረንስ ቱሪዝም እንዲስፋፋ፣ አዳዲስ ፓርኮች እንዲለሙ፣ ቅርሶች የቅርሱ ባለቤት የሆነው ህዝብ እንዲያስተዳድራቸው በማድረግ እና የቱሪዝም ልማቱን የሚያግዝ የብድር ስምምነት በማድረግ ዘላቂ የቱሪዝም ልማት ላይ በማተኮር፣ በርካታ የባህል ልውውጥ መድረኮችን ሀገራችን እንድትሳተፍ በማስቻል ያበረከቷቸው ተግባራት የሚወደሱ ናቸው፡፡

የሀገሬ ሚዲያ ኮሙኒኬሽን እና የቱባ መጽሔት ባልደረቦች በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማንን ሀዘን እየገለጽን ለባለቤታቸው፣ለትግል ጓዶቻቸው እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን፡፡

No comments:

Post a Comment