Friday, August 8, 2014


የፎቶና ቪዲዮ ባለሙያዊ አዚዝ አህመድ ድንቅ ሥራዎች ተመረቁ፡፡
 

ፕሮፌሽናል የጉዞ ፎቶ ግራፈሩና የቪዲዮ ባለሙያ የሆነው አዚዝ አህመድ በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ያነሳቸው የአእዋፍ ፎቶ ምስሎችና የሀገራችንን የተፈጥሮ ሀብቶች የሚያሳየውን የአጭር ድምጽና ምስል የቱሪዝም ዘጋቢ ፊልሙን ትናንት ነሐሴ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 9፡30 ላይ በአዲስ አበባ ካፒታል ሆቴል አስመርቋል፡፡

ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ይህ በኢትዮጵያዊ በዚህ መልኩ ሲሰራ የመጀመሪያ ሊባል የሚችለው ድንቅ ስራ ክቡር አቶ አሚን አብዱልቃድር የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ ክቡር አቶ እውነቱ ብላታ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ እንዲሁም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ዶ/ር ይናገር ደሴ በተገኙበት ተመርቋል፡፡

የጉዞ ፎቶግራፈሩ ጥንካሬ እውን ያደረጋቸው እነኚህ የኢትዮጵያን እምቅ የተፈጥሮ መስህቦች የሚያስተዋውቁ ስራዎች በሀገራችን ቱሪዝም ልማት ጎብኚዎችን በመሳብ የሚኖራቸው ፋይዳ ከፍተኛ ነው፡፡ ዶክመንተሪውም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአየር መንገደኞች በመቅረብ ላይ ያለ መሆኑን ስራውን ከደገፉት አንዱ የሆኑት የፍራንክፈርት ዙኦሎጂካል ሶሳይቲ ሃላፊ ዶ/ር ዘላለም ገልጸዋል፡፡

አዚዝ አህመድ በተለየ መልኩ ትኩረታቸውን በአእዋፍና ተፈጥሮ መስህቦች ዙሪያ አድርጎ በመስራት ስኬታማ ከሆኑ ኢትዮጵያዊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች አንዱ ነው፡፡  

No comments:

Post a Comment