Thursday, August 21, 2014


የአሸንዳ በዓል ዓመታዊ ኩነት በሰሜናዊቷ መቐለ መከበር ጀምሯል፡፡

ቱባ-መቐለ
 

በየዓመቱ የአሸንዳ በዓል በድምቀት የሚከበርባት የትግራይ ክልል መዲና ዘንድሮም በተመሳሳይ መልኩ በዓሉን ለማክበር ሰፊ ዝግጅት ስታደርግ ቆይታለች፡፡ ዛሬ ነሐሴ 15 ቀን 2006 ዓ.ም የአሸንዳ በዓል ዓመታዊ ኩነት ጀምሯል፡፡ ጠዋት በሚላኖ ሆቴል ለግማሽ ቀን በአሸንዳ ላይ የመከረው ሲምፖዚየምም የዚሁ ዝግጅት አካልና በትግራይ ባህልና ቱሪዝም ኤጀንሲ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከሰዓት ደግሞ የመቐለ ጎዳናዎች በአሸንዳ ጨፋሪዎች ይደምቃሉ፡፡ ነገ የሚከናወነው ዋናው የአሸንዳ በዓል ዝግጅት ነው፡፡
 

No comments:

Post a Comment