Friday, March 3, 2017

121ኛው የአድዋ ድል በዓል በብሄራዊ ደረጃ ለመጀመሪያ ግዜ በአድዋ ከተማ ተከብሯል፡፡








121ኛው የአድዋ ድል በዓል በብሄራዊ ደረጃ ለመጀመሪያ ግዜ በአድዋ ከተማ ተከብሯል፡፡ የአድዋ 121 የድል በዓል በአድዋ ከተማ ጦርነቱ በተከናወነበት የሶሎዳ ተራራ ግርጌ በሀገር ዓቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ግዜ ‹‹ የአድዋ ድል ብዝኃነን ላከበረቻት  ኢትዮጵያ ድህነትን ለማሸነፍ የሚያስችል ህያው አብነት ነው››!! በሚል መሪ ቃል ተከብሯል፡፡
በክብረ በዓሉ የኢ.ፌ.ድ.ሪ ፕሬዝደንት / ሙላቱ ተሾመ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ አባይ ወልዱ  እንዲሁም የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ሚኒስቴር / ሂሩት /ማርያምን ጨምሮ ሌሎች ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ተገኝተው የበዓሉ ተካፋይ ሆነዋል፡፡ ዶ/ ሙላቱ በንግግራቸው የአድዋ ድል በዓል የኢትዮጵያ ህዝቦች ድል ከመሆኑ ባለፈ የመላው የጥቁር ህዝቦች ድል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በበዓሉ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ አርበኞች ማህበር ፕሬዘዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ ወጣቱን የሚያነሳሳና የዘመኑን ጀግንነት የሚያወሳ ንግግር በማድረግ በዓሉ በዚህ ሁኔታ መከበሩ እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል ፡፡ በተጨማሪም የአድዋ ድል የአፍሪካ ህዝብ ድል መሆኑን በሚያንጸባርቅ መልኩ በቦታው የተገኙት የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝደንት ታቦ ምቤኪ ባደረጉት ንግግር የአድዋ ድል በዓል ለበርካታ አፍሪካ ሀገራት ህዝቦች ነጻነት ተምሳሌት መሆኑን እና ነጭ ቀኝ ገዢዎች በአፍሪካ ሲያዛምቱት የቆየውን የበላይነት አመለካከት የሻረ ታላቅ የፓን አፍሪካ ንቅናቄ መነሻ ነው፡፡ በተጨማሪም የፓን አፍሪካ ዩንቨርስቲ መከፈቱ አፍሪካውያንን ያነቃቃል ብለዋል፡፡ ምንም እንኳን በስፍራው ባይገኙም በቅርቡ ቦታቸውን ለተተኪው  ያስረከቡት የቀድሞዋ የአፍሪካ ህብረት ኮምሽነር / ኒኮሳዛና ዲላሚኒ ዙማ በዓሉን በማስመልከት ለመላው የኢትዮጵያ ብሎም የአፍሪካ ህዝብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በሌላ መልኩ በዓሉን በመንተራስ የህዳሴ ግድብ አዲስ የገቢ ማስገኛ ንቅናቄ ምክረ ሀሳብ ይፋ የተረደ ሲሆን በቀጣዩ ወር መጋቢት 17 ቀን 2009 ዓ.ም. በመንግስት በይፋ ለህዝብ ተዋውቆ ወደ ስራ እንዲገባ እንደሚደረግ ተገልጾል፡፡  የባህልና ቱሪዝም ሚኒስተር የአድዋ ድል በዓልን ከመምራት ባለፈ በስፍራው የአድዋ ጦርነት መታሰቢያ ሙዚየም ለመገንባት እቅድ መያዙንና ለእቅዱ እውን መሆን ጠንክሮ እንደሚሰራ ሚኒስትሯ / ሂሩት /ማርያም ተናግረዋል፡፡

No comments:

Post a Comment