Thursday, April 23, 2015

አራተኛው ዓለም አቀፍ የቱሪዝም የንግድ ትርኢት አውደ ርዕይ
ዛሬ ተከፈተ፡፡

በአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አዘጋጅነት የሚሰናዳውና ዘንድሮ ከሚያዝያ 15 እስከ 19/2007 ዓ.ም የሚቆየው አራተኛው ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ንግድ ትርኢት በኤግዚቢሽን ማዕከል ዛሬ ከሰዓት በኋላ በድምቀት ተከፍቷል፡፡

የንግድ ትርኢቱን አዲሱ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅትና 50ኛ ዓመት ኢዩቤልዩውን እያከበረ ያለው የኢትዮጵያ ቱሪስት ንግድ ስራ ድርጅትን ጨምሮ በርካታ አስጎብኚ ድርጅቶች፣ የአዲስ አበባ አስጎብኚ ማህበር፣ የተለያዩ ሆቴሎች፣ የእደ-ጥበብ አምራቾች፣ የክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮዎች ተሳትፈውበታል፡፡ አውደ ርዕዩ ለቀጣዮቹ አምስት ቀናት ለጎብኚዎች ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡

No comments:

Post a Comment