Friday, December 7, 2012


7ኛው የብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን
የዋዜማ በዓል ዛሬ በድምቀት ይከበራል፡፡

ሀሚኮ፡-
ከባህር ዳር ከተማ
የአማራ ክልሏ መዲና ባህር ዳር እያስተናገደችው ያለው 7ኛው የብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ዝግጅት ቀጥሏል፡፡ በባህር ዳር ዩንቨርስቲ ፔዳ ጊቢ አዳራሽና በአዲሱ የክልሉ ምክር ቤት መሰብሰቢያ እየተካሄደ ያለው ሲምፖዚየም ዛሬ ግማሽ ቀን በተናጥል ቀጥሎ ከሰዓት በኃላ 10፡00 ሰዓት ላይ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በወጣው መርሀ ግብር መሰረት ምሽቱን በጣና ሀይቅ ላይ የጀልባ ትርኢት የሚቀርብ ሲሆን በባህር ዳር ከተማ ጎዳናዎች ላይ የብሄር ብሄረሰብ ባህል ቡድን አባላት የባህል ትእይንት ያቀርባሉ፡፡ በባህር ዳር ስታዲየም ነገ የሚከበረውን አብይ በዓል በማስመልከት ዛሬ ምሽቱን ደማቅ የዋዜማ ዝግጅትና የርችት ተኩስ ይኖራል፡፡

No comments:

Post a Comment