Wednesday, December 5, 2012


 
ባህር ዳር በከፍተኛ ሁኔታ ደምቃለች፤

7ኛው የብሄሮች ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን ዝግጅት ተጀምሯል፤

እንግዶች እየገቡ ነው፤ ምናልባትም እስከዛሬ በክልሉ ተዘጋጅተው ከነበሩ ኩነቶች የበለጠ ደማቁ ኩነት ሳይሆን አይቀርም፤

ከ100 በላይ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ታድመውበታል፤

የአማራ ክልል እርእሰ ከተማ የሆነችው የጣና ዳሯ ባህር ዳር በመብራት ባጌጡ ዘንባባዎቿ ተሞሽራ ከእስዛሬው የተለየ ደማቅ ሀገራዊ ኩነት እያስተናገደች ነው፡፡ 50 ሺ የሚደርስ ተመልካች የሚይዘው የባህር ዳር ስቴዲየም ለበዓሉ ማስተናገጃ ከተመረጡ ስፍራዎች አንዱ ነው፡፡ አዲሱና አጠቃላይ ከ ግማሽ ቢሊየን ብር በላይ የሚፈጀው የክልሉ የስብሰባ አዳራሽ የተወሰነው ክፍል ተጠናቋል፡፡ 2250 የሚበልጥ ታዳሚ በምቹ ሁኔታ ያስተናግዳል፡፡ የበዓሉ አካል የሆነው አንዱ ሲምፖዚየም በዚሁ አዳራሽ ይካሄዳል፡፡

በዓሉን የሚታደሙትና ባህላዊ ትእይንት የሚያቀርቡት የብሄር ብሄረሰብ ልኡካን ቡድን ወደ ከተማዋ ሲገቡ በባህር ዳር ከተማ ህዝብ ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን በዓሉ በተለየ ሁኔታ ከነገ ህዳር 27 ጀምሮ በድምቀት ይከበራል፡፡

 

No comments:

Post a Comment