Sunday, June 24, 2012


በመሰሮ ኢበሌን በሰሮ

እንደ ስልጤ ያያም ኢልቅ/ የዘመን አቆጣጠር/ መሰሮ 1/ ሰኔ 20/

 የስልጤ የዘማን ኢጋኘ አያም/ዘመን መለወጫ

ያያም ኢልቅ ይሉታል የቀን አቀማመር ስልት ዘዴአቸውን፡፡ በደቡብ ክልል የሚገኙት ስልጤዎች የራሳቸው የቀን አቀማመር ካላቸው የሃገራችን ህዝብ መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ ይህ ወቅት የዓመቱ የመጨረሻ ወር ነው እንደ ስልጤዎች የቀን አቀማመር ሰኔ 20 ዓዲስ አመታቸው ነው፡፡ መሰሮ 1 ይሉታል እነሱ፡፡ ዘንድሮም በእለተ አርጴ/ረዕቡ/ ሰኔ 20 የሚውለው የስልጤ የዘመን መለወጫ ለስልጤዎች አዲስ አመታቸው ነው፡፡

በአሁኑ ወቅት በዘመን አቆጣጠሩ ላይ የሚደረጉ ጥናቶች የተጀመሩ ሲሆን የዘመን ቀመሩ መነሻ..መሰረት ያደረጋቸው ዋና ዋና መገለጫዎችና ሌሎች ሚስጥራቱ  ዙሪያ ካተኮሩት ጥናቶች በመነሳት ስለ አቀማመሩ ሰፊ መረጃ ይገኛል የሚል እምነት አለ፡፡




                                                           ለመላው የስልጤ ህዝብ ሀበይ ለሀጂሲ ዘማን በወገሬት አጄጄሙ! ብለናል

No comments:

Post a Comment