Monday, January 23, 2012


ጎንደር አይረሴ አስደናቂ የጥምቀት በዓል
የጎንደር ከተማ ወጣት የመንፈሳዊ ማኅበራት ጥምረት አባላት ውበት፣ኢትዮጵያዊነት እና ሃገር ተረካቢ ትውልድነት የተመሰከረበት በዓል
ከ100 ሺ ያላነሰ ጎብኚ ጎብኝቶታል፡፡
አቢሲኒያ የበረራ አገልግሎት ከሰማዩ ላይ እየቀዘፈ ከተራውና ጥምቀቱን አድምቆታል፡፡
የቦንጋ ከተማ ልኡክ በኢትዮጵያን በጎንደር ዝግጅት ላይ በመታደም ካፋ የቡና መገኛ ምድር መሆኑን አስተዋውቋል፡፡ ለጋኪ ሼሮቾ ምድር እንግዶች ጎንደር የአጼ ፋሲል ቤተ መንግስት ቅርጽን አበርክታላቸዋለች፡፡
በርካታ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት የታደሙበትን የዘንድሮን ኢትዮጵያን በጎንደር የአጼ ቴዎድሮስ ሐውልት ምርቃት አድምቆታል፡፡
ህይወት በአብያተ መንግስታት ግቢ በሚል የተዘጋጀው ትእይንት በአጼ ፋሲል ዘመን የቤተ-መንግስቱ ህይወት ምንይመስል እንደነበር የሚያሳይ ሲሆን በተመለከቱት ጎብኚዎች ዘንድ ከፍተኛ ስሜትን ፈጥሯል፡፡

No comments:

Post a Comment