Thursday, October 20, 2016



አዲሱ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ብራንድ እና ቀጣዩ የመገናኛ ብዙኃን ሚና

=====================================
ኢትዮጵያ የመለዮ ስያሜውን LAND OF ORIGINS ያደረገ አዲስ የቱሪዝም አርማ እና መለዮ ስያሜ ይፋ አድርጋለች፡፡ በቅርቡ በኢትዮጵያ ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጉት አዲሱ የመለዮ ስያሜ ግማሽ ምዕተ ዓመት ያክል የአስራ ሦስት ወር ጸጋ በሚል ሲያገለግል የኖረውን ብራንድ ስያሜ የሚተካ ነው፡፡

Friday, October 14, 2016


የመስቀል በዓል አከባበር በክስታኔ ቤተ-ጉራጌ
ጢያ ትክል ድንጋይ-ሶዶ ወረዳ
 

የመስቀል በዓል የተራራቁ የሚቀራረቡበት፣ የተነፋፈቁ ናፍቆታቸውን የሚወጡበት፣ ያለፈው ጊዜ ምን እንደሚመስል መጪው ጊዜ ምን መሆን እንዳለበት የሚወስኑበት ለክብረ በዓሉ በሰላም ላደረሳቸው ፈጣሪያቸው ምስጋና የሚያቀርቡበት ለወደፊቱም መልካም ምኞታቸውን የሚገልፁበት አጋጣሚ ነው፡፡ መስቀል የክስታኔ ቤተ-ጉራጌ ማህበረሰባዊ ልማዱን ከትውልድ ትውልድ ከሚያስተላልፍባቸው ሀገራዊ ልማዶች መካከል አንዱ በዓል ነው፡፡

Saturday, September 10, 2016


ጎፋ ጋዜ ማስቃላ 2009 በዛላ ወረዳ ይከበራል፡፡
 

በጎፋ ብሔረሰብ ዘንድ በድምቀት የሚከበረው የመስቀል በዓል ጎፋ ጋዜ ማስቃላ 2009 በዛላ ወረዳ በድምቀት ይከበራል፡፡ ከመስከረም 9-10 ቀን 2009 ዓ.ም. የሚከበረው ይህ በዓል በጎፋ ብሔረሰብ የተለዩ እሴቶች የሚደምቅና ጊያ ካንሶ በሚባለው የመስቀል በዓል ሽኝት ሥነ-ሥርዓት የሚታጀብ ነው፡፡

Friday, August 26, 2016


አሸንዳ 2008 በዓል በመቐለ በድምቀት ተከብሯል፡፡
Photo; Ashenda festival in Mekelle

አሸንዳ 2008 ባህላዊ ኩነት በትግራይ ክልል ርዕሰ መዲና በመቐለ በድምቀት ተከብሯል፡፡ ከነሐሴ 15 እስከ ነሐሴ 18 ቀን 2008 ዓ.ም. በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ሲከበር የቆየው ይህ በዓል ከመቐለ ከተማ ውጪ በተንቤን አብይ አዲም በድምቀት መከበሩን ለማወቅ ችለናል፡፡


ሻደይ 2008 ፌስቲቫል በድምቀት ተከበረ፡፡
Photo: shaday festival 2016 wagehimera zone
ሻደይ 2008 የባህል ፌስቲቫል በዋግኽምራ ብሔረሰብ ዞን መዲና በሰቆጣ ከተማ ከነሐሴ 14 ቀን እስከ 16 2008 ዓ.ም. በድምቀት ተከብሯል፡፡"የሻደይ ባህላችን ለዘላቂ ልማታችን" በሚል የተከበረው ይህ በዓል የተለያዩ ዝግጅቶችን ያካተተ ሲሆን በርካታ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላችው እንግዶች የታደሙበት ነው፡፡

Thursday, August 4, 2016


                       ኦይዳ ወረዳ
 

የኦይዳ ወረዳ በጋሞ ጎፋ ዞን ከሚገኙ አስራ አምስት ወረዳዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን የወረዳው ዋና ከተማ ሸፊቴ ይባላል፡፡ ወረዳው የተመሰረተው በ1998 ዓ.ም. ነው፡፡ ኦይዳ ማለት ለም ማለት ሲሆን የብሔረሰቡና የወረዳው መጠሪያም ነው፡፡ ወረዳው በሃያ ቀበሌያት የተዋቀረ ሆኖ በደቡብ ኡባ ደብረ ፀሀይ፣ በሰሜን ገዜ ጎፋ፣ በምዕራብ ሰሜን አሪ እና በምስራቅ ደግሞ ደንባ ጎፋ ወረዳ ያዋስኑታል፡፡

Wednesday, August 3, 2016


        የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የህዝብና ዓለም አቀፍ ዳይሮክተሬት በ2008 ዓ.ም. አፈጻጸም ተሸላሚ ሆነ፡፡

በመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት በዘርፍ ከሚገኙ የፌዴራል የኮሙኒኬሽን አደረጃጀቶች መካከል የ2008 ዓ.ም. አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላመጡ እውቅና ተሰጥቷል፡፡