አሸንዳ 2008 በዓል በመቐለ በድምቀት ተከብሯል፡፡
አሸንዳ 2008 ባህላዊ ኩነት በትግራይ ክልል ርዕሰ መዲና በመቐለ በድምቀት ተከብሯል፡፡ ከነሐሴ 15 እስከ ነሐሴ
18 ቀን 2008 ዓ.ም. በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ሲከበር የቆየው ይህ በዓል ከመቐለ ከተማ ውጪ በተንቤን አብይ አዲም በድምቀት መከበሩን
ለማወቅ ችለናል፡፡
ነሐሴ 15 ቀን 2008 ዓ.ም. ጠዋት በመቐለ አክሱም ሆቴል የተደረገው ዓመታዊው የአሸንዳ ሲምፖዚየም በአሸንዳ በዓል ዙሪያ በስፋት መክሯል፡፡ የጎዳና
ላይ የካርኒቫል ትእይንቱን ከየዞኑ የተውጣጡ የባህል ተጨዋቾች አድምቀውታል፡፡

የበዓሉ ዋና አካል በሆነው የዛሬው ዝግጅት እንደ ትግራይ ልጃገረዶች ሁሉ የውጪ ዜጎችም የአሸንዳ ልብስ ለብሰው የታዩበት
ነበር፡፡ የአሸንዳ በዓል ማጠናቀቂያ የነበረውና ነሐሴ 18 ቀን 2008 ዓ.ም. ምሽት በድምቀት የተከበረው የማጠቃለያ ዝግጅትም
እጅግ ደማቅና የተለየ ነበር፡፡
No comments:
Post a Comment