Friday, July 20, 2012


ቱሪዝም በዳዉሮ
ጨበራ ጩርጩራ ብሄራዊ ፓርክ


የዳዉሮ ዞን  ከኢትዮጵያ ዉብ ገፅታ ማሳያዎች አንዱ ነዉ፡፡ ዞኑ በደቡብ ክልል የሚገኝ ሲሆን የዞኑ ዋና ከተማ ታርጫ ትባላለች፡፡ ታርጫ ገስጋሽ ነገር ግን በሚሌኒየሙ ከተወለዱ ከተሞች አንዷ ናት፡፡ ከሐዋሳ በ282 ኪ.ሜ ከአዲስ አበባ ደግሞ በሻሸመኔ አድርገዉ በወላይታ ሶዶ የሚጓዙ ከሆነ 455 ኪ.ሜ ከአዲስ አበባ በሌላኛዉ መንገድ በጅማ አርገዉ የሚጓዙ ከሆነ ደግሞ በ479 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚያገኟት ከተማ ስትሆን ከተማዋ በየግዜዉ እያስመዘገበች ባለዉ እድገት ሳቢያም የብዙዎችን ትኩረት ስባለች፡፡

      በደቡብ ከጋሞ ጎፋ በምዕራብ ከኮንታ ልዩ ወረዳ በሰሜን ምዕራብ ከኦሮምያ ክልል በሰሜን እስከ ሰሜን ምስራቅ ከከንባታ ጠንባሮ ዞን በምስራቅ ከወላይታ ዞን ይዋሰናል፡፡ ከሰሜን ምዕራብ እስከ ደቡብ ጫፍ ድረስ በጎጀብና በኦሞ ወንዞች ተፋሰስ የተከበበዉ የዳውሮ ዞን የብዙ እሴቶች ማዕከል እና እንብርት ነዉ፡፡ ከአምስት በላይ በሆኑ ብሄረሰቦች መከበቡ ዳውሮን ልዩ የባህል አምባ ያደርገዋል፡፡

Wednesday, July 4, 2012


ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸሙን ገመገመ

ብዙዎቹ ተግባራት የተሻለ አፈጻጸም አስመዝግበዋል፡፡

ፓርኮችን በመጎብኘት ረገድ የሃገር ውስጥ ጎብኚዎች ቁጥር እየጨመረ ነው

የባህል ልውውጥና ግንኙነት አፈጻጸሙ 108 በመቶ ሆኗል….

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የዘጠኝ ወራት አፈጻጸሙን በመገምገም የአፈጻጸም ልኬቱን በቁጥርና በመቶኛ አስቀምጧል፡፡ በዘጠኝ ወሩ አስራ ሶስት የባህል ልውውጥና ግንኙነት ለማከናወን ታቅዶ የነበረ ሲሆን አስራ አራት ለማከናወን በመቻሉ ከእቅዱ ያለፈና 108 በመቶ የሆነ ውጤት ለማስመዝገብ ተችሏል፡፡ በግማሽ ዓመቱ ብቻ 9 የባህል ልውውጥና ግንኙነት ለማከናወን ታስቦ 11 ለማከናወን ሲቻል አንድ ባህላዊ የሙዚቃ ኪነት ቡድን በውጪ ሃገር ትርኢት ለማቅረብ በታሰበው መሰረት በህንድ ሶስት ከተሞች ትርኢቱን በማሳየት ሃገሪቱንና የህዝቦቿን እሴት በሚገባ ለማስተዋወቅ ተችሏል፡፡

በዘጠኝ ወራቱ አፈጻጸም የቱሪስቶች ቁጥር 474,249 ደርሷል፤ ይህም ከእቅዱ አንጻር 88 በመቶ ሲሆን በቋሚ ኤግዚቢሽን ጎብኚዎች ረገድ 106,084 የሀገር ውስጥና የውጪ ጎብኚዎች በብሄራዊ ሙዚየም የቋሚ ኤግዚቢሽን የማስጎብኘት እድል ተፈጥሯል፡፡ በሃገር ውስጥ ጎብኚዎች ገረድም በተለይም ፓርኮችን በመጎብኘቱ አበረታች ውጤት የተመዘገበ ሲሆን 30,110 የሃገር ውስጥ ጎብኚዎች የሃገሪቱን ፓርኮች ጎብኝተዋል፡፡ የሴቶቹ ቁጥር ደግሞ 12,405 ነው፡፡ ይህ ቁጥር 42,246 የውጪ ጎብኚዎች ቁጥር ጋር ሲነጻጸር የሃገር ውስጥ ጎብኚዎች ፓርኮችን የመጎብኘት ባህል እያደገ መምጣቱን ያሳያል፡፡

በአጠቃላይ በአለፍት ዘጠኝ  ወራት ከቱሪስቶች 371,811,216 የአሜሪካን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡ የአንድ ቱሪስት አማካኝ የቆይታ ግዜ 6.5 ሲሆን የቀን ወጪው ደግሞ 120.6 የአሜሪካን ዶላር መሆኑን ያገኘንው መረጃ ያመላክታል፡፡


Sunday, June 24, 2012


በመሰሮ ኢበሌን በሰሮ

እንደ ስልጤ ያያም ኢልቅ/ የዘመን አቆጣጠር/ መሰሮ 1/ ሰኔ 20/

 የስልጤ የዘማን ኢጋኘ አያም/ዘመን መለወጫ

ያያም ኢልቅ ይሉታል የቀን አቀማመር ስልት ዘዴአቸውን፡፡ በደቡብ ክልል የሚገኙት ስልጤዎች የራሳቸው የቀን አቀማመር ካላቸው የሃገራችን ህዝብ መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ ይህ ወቅት የዓመቱ የመጨረሻ ወር ነው እንደ ስልጤዎች የቀን አቀማመር ሰኔ 20 ዓዲስ አመታቸው ነው፡፡ መሰሮ 1 ይሉታል እነሱ፡፡ ዘንድሮም በእለተ አርጴ/ረዕቡ/ ሰኔ 20 የሚውለው የስልጤ የዘመን መለወጫ ለስልጤዎች አዲስ አመታቸው ነው፡፡

በአሁኑ ወቅት በዘመን አቆጣጠሩ ላይ የሚደረጉ ጥናቶች የተጀመሩ ሲሆን የዘመን ቀመሩ መነሻ..መሰረት ያደረጋቸው ዋና ዋና መገለጫዎችና ሌሎች ሚስጥራቱ  ዙሪያ ካተኮሩት ጥናቶች በመነሳት ስለ አቀማመሩ ሰፊ መረጃ ይገኛል የሚል እምነት አለ፡፡




                                                           ለመላው የስልጤ ህዝብ ሀበይ ለሀጂሲ ዘማን በወገሬት አጄጄሙ! ብለናል

Tuesday, June 19, 2012


ብሄራዊ የቱሪዝም መማክርት ጉባኤ ውይይቱን አካሄደ

ወቅታዊ ጉዳዮች ተነስተዋል፤

የቱሪዝም ሥነ-ምግባር መምሪያው ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

ዜና፡- ሀሚኮ

ትናንት ሰኔ 12 ቀን 2004 ዓ.ም ሙሉ ቀን በአዲሱ ራንድ ሰን ብሉ ሆቴል የተካሄደው የብሄራዊ የቱሪዝም መማክርት ጉባኤ በዋናነት በዓለም ባንክ አማካኝነት የተዘጋጀውንና የሃገራችን ቱሪዝም አጠቃላይ ጠቀሜታዊ ይዘት ላይ ያተኮረው የጥናት ጥቅል ውጤት ላይ ውይይት አድርጓል፡፡

Friday, June 15, 2012

አሁን አየ ዓይኔ     
የቱሪዝም ንግድ ትርኢት በአዲስ አበባ
የሃገራችን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ለዘመናት ይጓዝበት ከነበረው ከርፋፋና ቀርፋፋ አካሄድ ወጥቶ ያለፍትን ጥቂት ዓመታት ሶምሶማ ወደሚባል ፍጥነት እየገባ መጥቷል፡፡ የሁልም ጊዜም ቁጭታችን ባለን ነገር ባለመጠቀም ከሌላቸው ህዝቦች ውራ ቁጥር መግባታችን ነበር፡፡ ስለአለን ነገር እንኳን ስናስብ ከሌላው የምንልቅበት በርካታ ነገር አለ፤ እኛ ያለን ሃብት እውቀት ገንዘብና ቴክኖሎጂ ሊያመጡት አይችሉም፤ ብዝኃ- ህይወትን ከባህል ጋር፣ ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሮአዊ ሃብቶችን ታድለናል፡፡ ለጥቁር ህዝብ ተምሳሌት የሚሆን ትናንትና ያለን ህዝቦች ነን፤ ይህንን ተጠቅመን መጠቀም አቅቶን ኑሯል፤ እንደውም አናወራውም ስለራስ ማውራት መታበይ ነው የሚል ብሂል አለን፤ ስለራስ ካልተወራ ውጤት የማይገኝበት የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ልባችንን የምናሳርፍበት አልሆን ያለውም ለዚህ ነው፡፡

Thursday, June 7, 2012


                                       ራስ ግንብ
ይህ ቤተመንግስት የተገነባው በከፍታ ቦታ ላይ ሲሆን ከፋሲል ቤተ-መንግስት በስተሰሜን በኩል 300 ሜትር ርቀት ላይ ነው፡፡  ይህ ቤተመንግስት ባለሁለት ፎቅ ሆኖ ከመሰረቱ ሰፊና ወፍራም ግንባታ ያለው ሲሆን ወደላይ እየቀጠነ የሚሄድ ነው፡፡

ሁለት ወታደሮች (ማማዎች) ሲኖሩት ሶስተኛው ግን በባለ አራት ማዕዘን ማማው መሐል ይገኛል፡፡ እንደነዚህ ዓይነት የአሰራር ስልቶች በዘመኑ ሰቀላ ግንብ ወይም ከበሮ ግንብ በመባል ታወቃሉ፡፡ በተለይ አራተኛውና ትልቁ ማማ (Tower) ይህ ቤተመንግስት ግርማ ሞገሱ የበለጠ ጎልቶ እንዲታይ አድርጎታል፡፡ ይህ ሁሉ ውበትና የአሰራር ጥበብ የፈሰሰበት ቢሆንም  ከአፄ  ፋሲል  ቤተመንግስት (ግንብ) በመጠኑ ያነሰነው፡፡ ነገር ግን በቅርጹና በአሰራር ጥበቡ ተመሳሳይነት አለው፡፡

                  ራስ ግንብ  ሙዚየም
               RAS GENB MUSUME