Tuesday, June 5, 2012

                 አንድ ሺሕ አምስት መቶ ዓመት ያስቆጠረው የአቡነ ገሪማ ገዳም
                                              ሙዚየም ተመረቀ
አንድ ሺሕ አምስት መቶ ዓመታት ባስቆጠረው የአቡነ ገሪማ ገዳም የተሠራው አዲስ ሙዚየም ግንቦት 18 ቀን 2004 ዓ.ም. ተመረቀ፡፡
በትግራይ ክልል በዓድዋ ወረዳ የሚገኘውና ከገዳሙ እኩል ዕድሜ 1500 ዓመታትን ያስቆጠረ የወንጌል መጻሕፍትና ጥንታውያን ቅርሶች ላሉበት ገዳም ዘመናዊ ሙዚየሙ የተገነባለት ከ400 ሺሕ ብር በላይ ወጪ ነው፡፡

መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቱያን የቅርስ ጥበቃና ምዝገባ የቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምርያ ኃላፊ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የፈረንሣይ መንግሥት በሰጠው ከ400 ሺሕ ብር በላይ ዕርዳታ መሠረት ጥንታዊው ሕንፃ ታድሶና ተዘጋጅቶ ለቤተ መዘክር አገልግሎት እንዲውል ተደርጓል፡፡

Monday, June 4, 2012


ሰኔ ሰላሳ የሚያሳድዳቸው የባህል ፌስቲቫሎች

ደማቁ የእሬቻ በዓል
ይሄ ሰኔ ሰላሳ የሰነፍ ተማሪ  የምጥ ቀን ነበር…አሁን አሁን ተቋማት.. በጀት ዓመታቸውን ለመጨረስ…ከፋይዳው ይልቅ ለሪፖርት የሚሆን ተግባር ለማከናወን ተገልጦ የሚታይ ጉድ እየተመለከትን ነው፡፡ የባህል ፌስቲቫሎች በባህል ልማት በቱሪዝም ምርትነትና በገጽታ ግንባታ፤ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ ይህንንም በእጅጉ እናበረታታለን፤ ከዳር ዳር የባህል ፌስቲቫሎች እንዲናኙ ምኞት ብቻ ሳይሆን ይፈጸም ዘንድ እንተጋለን፤ግን እንዴት ? ዓላማስ አለው ወይ…ግቡስ ምንድን ነው እነዚህን ሁሉ ጥያቄዎች ሊመልስ ይገባዋል፡፡

Tuesday, May 29, 2012



የአቡኑ ከተማ

በሰሜን ሸዋ ዞን .. ከደጋማው የመንዝ ምድር .. ተፈጥሮው በብዙ ከሚተርክበት .. መልከአ-ምድር መሃል በዚያ ንጹህ አየር በሚሳብበት ውብ ምድር የሚገኝ ጥንታዊና ታሪካዊ ስፍራ ነው፡፡

ሰላድንጋይ የዚህ ድንቅ ስፍራ መጠሪያ ነው፡፡ ከሰሜን ሸዋ ዞን መዲና ከደብረ ብርሃን ከተማ በ75 ከ.ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ሰላ ድንጋይ ኢትዮጵያን ለ38 ዓመታት በፓትሪያሪክነት ያገለገሉት አባት የአቡነ ማቴዎስ የመንበር ጵጵስናቸው መቀመጫ ነበረች፡፡

 ግብጻዊው ፓትሪያሪክ አቡነ ማቴዎስ በዚሁ ስፍራ በ1875 ዓ.ም የማርቆስ ቤተ-ክርስቲያንን አሰርተዋል፡፡

Thursday, May 17, 2012


የሥነ-ጽሁፍ ሃብቶቻችን የቅርስነት ዋጋቸው….. በዜጎች ተመዝኖ ይሆን

ብራና
ቅርስ የአንድ ህዝብ ማንነት ነው፤ ከቅርሱ ጀርባ የቅርሱ ባለቤት የሆነው ህዝብ ባህል፣ የአኗኗር ዘይቤ፣እሴቶችና መገለጫዎቹ አሉ፡፡ ለዚህም ነው ቅርሶች ባለቤታቸው ከሆኑ ህዝቦች ህልውና ተለይተው የማይታዩት፡፡ ከቅርስ ጋር ተያይዞ በሃገራችን ያለው አስተሳሰብ ቅርስን ከሥነ-ህንጻ ጥበብ ጋር ብቻ በማቆራኘት የመፈረጁ ባህል ከዘርፍ ጋር በቂ ግንዛቤ በሌላቸው ሰዎች ብቻ ሳይሆን ባለሙያም በሆኑ አካላት ጭምር እየተስተዋለ ነው፤ ለዚህም ነው የጽሁፍ ቅርሶቻችን ስንል ስለ ጽሁፍ ሃብቶቻችንና ስለ ቅርስነት ይዘታቸው ማንሳት የፈለግንው፤

Sunday, May 13, 2012

calander/
ባሕረ-ሐሳብ በአለቃ ያሬድ ፈንታ


በስልጤ ህዝብ ባህል ዙሪያ ለዓመታት ተጠንቶ የተዘጋጀው የኬይረዲን ተዘራ መጸሐፍ ለህትመት በቃ፡፡
መጸሀፍ ዛሬ ግንቦት 5 ቀን 2004 ዓ.ም በኢትዮጵያ ባህል ማእከል በታላቅ ድምቀት ተመርቋል፡፡

ወጣቱ ኬይረዲን ተዘራ ግዜ ወስዶ፣ታሪክ አዋቂ የስልጤ ሽማግሌዎችን ቃለ-መጠይቅ አድርጎ፣በርካታ መዛግብትን አገላብጦ…ያዘጋጀው ይህ መጸሐፍ የብሄረሰቡን ባህልና ታሪክ በማስተዋወቅ ረገድ የጎላ ድርሻ እንደሚኖረው ብዙዎች ተንብየዋል፡፡ ኬይረዲን በተለያዩ ግዜያት በወራቤ ከተማ ይደረጉ በነበሩ የቋንቋ፣ባህልና ታሪክ ሲምፖዚየሞች ያቀርባቸው የነበሩ ጥናቶች የስልጤ ሽማግሌዎችን በመማረክ ለምርቃት አብቅተውታል፡፡