Wednesday, September 17, 2014


የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኒዓለም ሙዚየም
የልጅ እያሱ አልጋ
 

አዲስ አበባ ከሚገኙ 14 ሙዚየሞች አንዱ የቀጨኔ ሙዚየም ነው፡፡ ቀጨኔ ሙዚየም በአስተዳደር ጊዜያቸው ለህብረተሰቡ ኑሮ ምቹ ከመሆናቸው የተነሳ አቤቶ (ማር) የሚል ስያሜ የተሰጣቸው ልጅ እያሱ ከመቶ ዓመት በፊት  ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ካሳነፁ በኋላ የተቋቋመ ሙዚየም ነው፡፡ በሙዚየሙ ውስጥ ከሚገኙ ቅርሶች ብዙዎቹ የልጅ እያሱ የግል መገልገያ እቃዎች፣ ነዋየ ቅድሳት፣ አልባሳት እና የተለያዩ ነገስታት ስጦታዎች ይገኛሉ፡፡

በናና ጸማይ…..


 
በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ደቡብ ኦሞ ዞን ስር ከተዋቀሩት 8 ወረዳዎችና አንድ የከተማ አስተዳደር መካከል የበናና ፀማይ ወረዳ አንዱነው፡፡ የወረዳው ዋና ከተማ ቀይ አፈር ከዞኑ ዋና ከተማ ጂንካ በስተደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ በ42 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ወረዳው በሰሜን ከደቡብ አሪ እና ማሌ፣ በደቡብ ከሐመር ወረዳ፣ በስተምስራቅ ከኮንሶ በምዕራብ ከማጎ ፓርክ እና ሳላማጎ ወረዳ ጋር ይዋሰናል፡፡ በዞኑ ከሚገኙት 16 ብሔረሰቦች ውስጥ በዋናነት ሶስቱ ብሔረሰቦች የሚገኙት በዚህ ወረዳ ውስጥ ነው፡፡ እነዚህም የበና፣ የፀማይ እና የብራይሌ ብሔረሰቦች ናቸው፡፡

አፋር ያልተነገረላቸው ሁሉ አቀፍ የቱሪስት መስህቦች ቀጠና

የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በኢትዮጵያ ከሚገኙ 9 ክልሎችና 2 ከተማ መስተዳደሮች አንዱ ነው፡፡ ክልሉ ጂኦግራፊካሊ በሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያ በ39 14 እና 42 28 ሰሜን የኬክሮስ መስመርና በ8 49 እና በ14 30 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመሮች ይገኛል፡፡
Afar-
 

የአፋር ክልል በ5 አስተዳደራዊ ዞኖች 31 ወረዳዎችና በ1 ልዩ ወረዳ የተዋቀረ ነው፡፡ የቆዳ ስፋቱም 96,256 ስኩየር ኪ.ሜ ነው፡፡  እንደ ኢትዮጵያ ማእከላዊ ስታስቲክስ 2007 መረጃ መሰረት 1,411,920 ህዝብ ይኖርበታል፡፡ ከዚህም 86.6% በገጠር ቀሪው በከተማ የሚኖር ህዝብ ነው፡፡ አፋርኛ ቋንቋ የክልሉ የስራ ቋንቋ ሲሆን 90.8% ተናጋሪዎች አሉት፡፡

Tuesday, August 26, 2014


         አሸንዳ - የሰሜናዊቷ ኮከብ ከተማ ኮከብ ኩነት

 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች ዘንድ የጾመ ፍልሰታ ፍጻሜን ተከትሎ የሚከበረው የአሸንድዬ በዓል በዋናነት በሰሜን ኢትዮጵያ ከሚከበሩ መንፈሳዊ በዓላት መካከል የሚጠቀስ ነው፡፡ የአሸንዳ ባህላዊ ጨዋታ መጠሪያ የኾነው ቄጤማ ረዥምና ለምለም እንደ ቅጠል ሰፋ ያለ ሲሆን ቁመቱ 80 እስከ 90 . ይኾናል፡፡

የአሸንዳ በዓል በትግራይ ብሔራዊ ክልል የሚከበር በሀገራችን ከሚገኙ ኩነቶች አንዱ ነው፡፡ አሸንዳ ጥንታዊና የልጃገረዶች ባህላዊ በዓል ነው፡፡ በተለይም ከአዲስ አበባ በ783 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው የክልሉ መዲና መቐለ በየዓመቱ የምታስተናግደው ይህ ፌስቲቫል ከትግራይ ወጣቶች ባለፈ ጎብኚዎችም በጉጉት የሚጠብቁት ባህላዊ ትዕይንት ሆኗል፡፡

Thursday, August 21, 2014


የአሸንዳ በዓል ዓመታዊ ኩነት በሰሜናዊቷ መቐለ መከበር ጀምሯል፡፡

ቱባ-መቐለ
 

በየዓመቱ የአሸንዳ በዓል በድምቀት የሚከበርባት የትግራይ ክልል መዲና ዘንድሮም በተመሳሳይ መልኩ በዓሉን ለማክበር ሰፊ ዝግጅት ስታደርግ ቆይታለች፡፡ ዛሬ ነሐሴ 15 ቀን 2006 ዓ.ም የአሸንዳ በዓል ዓመታዊ ኩነት ጀምሯል፡፡ ጠዋት በሚላኖ ሆቴል ለግማሽ ቀን በአሸንዳ ላይ የመከረው ሲምፖዚየምም የዚሁ ዝግጅት አካልና በትግራይ ባህልና ቱሪዝም ኤጀንሲ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከሰዓት ደግሞ የመቐለ ጎዳናዎች በአሸንዳ ጨፋሪዎች ይደምቃሉ፡፡ ነገ የሚከናወነው ዋናው የአሸንዳ በዓል ዝግጅት ነው፡፡
 

Friday, August 8, 2014


የፎቶና ቪዲዮ ባለሙያዊ አዚዝ አህመድ ድንቅ ሥራዎች ተመረቁ፡፡
 

ፕሮፌሽናል የጉዞ ፎቶ ግራፈሩና የቪዲዮ ባለሙያ የሆነው አዚዝ አህመድ በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ያነሳቸው የአእዋፍ ፎቶ ምስሎችና የሀገራችንን የተፈጥሮ ሀብቶች የሚያሳየውን የአጭር ድምጽና ምስል የቱሪዝም ዘጋቢ ፊልሙን ትናንት ነሐሴ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 9፡30 ላይ በአዲስ አበባ ካፒታል ሆቴል አስመርቋል፡፡

ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ይህ በኢትዮጵያዊ በዚህ መልኩ ሲሰራ የመጀመሪያ ሊባል የሚችለው ድንቅ ስራ ክቡር አቶ አሚን አብዱልቃድር የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ ክቡር አቶ እውነቱ ብላታ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ እንዲሁም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ዶ/ር ይናገር ደሴ በተገኙበት ተመርቋል፡፡

የጉዞ ፎቶግራፈሩ ጥንካሬ እውን ያደረጋቸው እነኚህ የኢትዮጵያን እምቅ የተፈጥሮ መስህቦች የሚያስተዋውቁ ስራዎች በሀገራችን ቱሪዝም ልማት ጎብኚዎችን በመሳብ የሚኖራቸው ፋይዳ ከፍተኛ ነው፡፡ ዶክመንተሪውም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአየር መንገደኞች በመቅረብ ላይ ያለ መሆኑን ስራውን ከደገፉት አንዱ የሆኑት የፍራንክፈርት ዙኦሎጂካል ሶሳይቲ ሃላፊ ዶ/ር ዘላለም ገልጸዋል፡፡

አዚዝ አህመድ በተለየ መልኩ ትኩረታቸውን በአእዋፍና ተፈጥሮ መስህቦች ዙሪያ አድርጎ በመስራት ስኬታማ ከሆኑ ኢትዮጵያዊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች አንዱ ነው፡፡  

Wednesday, July 23, 2014


የሲዳማ ዘመን መለወጫ በዓል በሐዋሳ እየተከበረ ነው፡፡

የራሳቸው የቀን አቆጣጠር ካላቸው የሀገራችን ብሔሮች አንዱ የሆነውና በየዓመቱ በልዩ ድምቀት የዘመን መለወጫ በዓሉን የሚያከብረው የሲዳማ ብሔረሰብ የፍቼ በዓል በታላቅ ድምቀት በሐዋሳ እየተከበረ ነው፡፡


ዝግጅቱ በዋናነት ዛሬ ሐምሌ 16 ቀን ከሰዓት በኋላ በሲዳማ ባህል አዳራሽ በታላቅ ድምቀት መከበሩን የቀጠለ ሲሆን በዝግጅቱም ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ አቶ ሽፈራሁ ሽጉጤ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደሴ ዳልኬ እና የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የብሔረሰቡ ምሁራንና ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች ታድመውበታል፡፡
ዝግጅቱን በተመለከተ የሲዳማ ዞን ባህል ቱሪዝምና መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ሃላፊ አቶ ወርቅነህ ፍላቴ ሲናገሩ፤ ፍቼ በቅርብ ጊዜ ኢትዮጵያ በዩኔስኮ የምታስመዘግበው ዓለም አቀፍ ቅርስ ይሆናል ብለዋል፡፡
 
በዓሉ በነገው ዕለትም ቀጥሎ የሚውል ሲሆን የበዓሉ ዋና መዲና ሐዋሳ በዓሉን በከፍተኛ ዝግጅት እያስተናገደችው ነው፡፡