የዘንድሮ የዓለም የሙዚየም ቀን‹‹ ሙዚየሞችና ባህላዊ መልክዓ ምድር!››/ Museums and Cultural
Landscape/ በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ39ኛ ጊዜ
በአገራችን ለ14
ጊዜ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ተከበረ፡፡ 
በተፈጥሮአዊና
ባህላዊ የመልክዓ ምድር አያያዝና
አጠቃቀም ፣ በጥምር ደንና የግብርና ሥርዓት  በዓለም ቅርስነት ባስመዘገበው በደቡብ ብሔር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መከበሩ ልዩ ያደርገዋል፡፡  በክልሉ ከተማዎች
ማለትም  በሐዋሳ ፣ በአርባ ምንጭ ፣ በቱርሚ፣ በጅንካና በኮንሶ
አካባቢዎች ማዕከል በማድረግ ከግንቦት 06  
እስከ ግንቦት 12  2008 ዓ.ም የተለያዩ ፕሮግራሞች ተከናውነዋል፡፡
 

